Discover

Topics

ሶስቱ መሰረቶች

ሶስቱ መሰረቶች APK

ሶስቱ መሰረቶች APK

1.0 FreeAbdulsemed ⇣ Download APK (2.88 MB)

الأُصُولُ الثَّلاثَةُ
ሶስቱ መሰረቶች

ሸይኽ
ሙሐመድ ኢብኑ ዐብዲል ወህሃብ
ረሒመሁላህ

What's ሶስቱ መሰረቶች APK?

ሶስቱ መሰረቶች is a app for Android, It's developed by Abdulsemed author.
First released on google play in 4 years ago and latest version released in 4 years ago.
This app has 38.5K download times on Google play and rated as 4.50 stars with 130 rated times.
This product is an app in Books & Reference category. More infomartion of ሶስቱ መሰረቶች on google play
الأُصُولُ الثَّلاثَةُ
ሶስቱ መሰረቶች

ሸይኽ
ሙሐመድ ኢብኑ ዐብዲል ወህሃብ
ረሒመሁላህ
(1115 - 1206 ዓ.ሂ.)

መግቢያ

“አልኡሱሉ አሥሠላሣህ” እና “አልቀዋዒዱል አርበዕ” ኪታቦች በሱንኒው አለም ባሉ ሙስሊሞች ዘንድ ሰፊ እውቅና እና ተቀባይነት ያላቸው ኪታቦች ናቸው፡፡ ኪታቦቹ በውስጣቸው ከያዙት አንገብጋቢ የተውሒድ መልእክት በተጨማሪ አቀራረባቸው በራሱ እራሱን የቻለ ትልቅ ስርኣተ-ትምህርት ነው፡፡ እያንዳንዱ ነጥብ በቁርኣናዊ ወይም ሐዲሣዊ ማስረጃ መደገፉ በዚህ ስርኣተ- ትምህርት ውስጥ ያለፈ ትውልድ የትኛውንም እምነት ነክ ጉዳይ ያለ ማስረጃ ሊቀበል እንደማይገባው ፅኑ መልእክት አለው፡፡
በትርጉም ስራዬ ላይ በኪታቦቹ ውስጥ የተጠቀሱ የቁርኣን አንቀፆችን፣ ሐዲሦችን እና የዑለማእ ንግግሮችን መገኛቸውን ያሰፈርኩ ሲሆን ሐዲሦቹን ቡኻሪና ሙስሊም ከዘገቧቸው ውጭ ባሉት ላይ የታላቁን ሙሐዲሥ የሸይኹል አልባኒን ብይኖች አስፍሬያለሁ፡፡ አልፎ አልፎ ሀሳቦችን ያብራራሉ ብዬ ያሰብኳቸውን ማስታወሻዎች ከግርጌ አስፍሬያለሁ፡፡
ኪታቦቹን ለመማር ማስተማር ይበልጥ እንዲያግዝ በማለም ሙሉ ትርጉም ብቻ ከማድረግ ይልቅ ዐረብኛውን መልእክት ካሰፈርኩ በኋላ ቀጥሎ ትርጉሙን ያስከተልኩ ሲሆን ለጀማሪዎች እንዲያግዝ በማሰብም የዐረብኛ አናባቢ ምልክቶች (ሐረካት) እንዲኖሩ አድርጌያለሁ፡፡
ያለንበት ዘመን እንደ አሕባሽ ያሉ የጥፋት ሃይሎች ኢስላማችንን ለመናድ፣ ህዝባችንን በብልሹ እምነቶች ለመበከል ቆርጠው የተነሱበት ዘመን እንደመሆኑ ወላጆች ለልጆቻቸው ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ትኩረት ሊሰጡ የሚገባቸው ጊዜ ነው፡፡ ሁሌ እንደ አሸን እየፈሉ ያሉ የአስተሳሰብ ወረራዎችን ለመመከት ንቃተ-ህሊናን ማዳበር ቀዳሚው ምርጫ እንደመሆኑ ወላጆች ይህንን የትልቅ ዓሊም ትልቅ ስራ እና መሰል ጤናማ ኪታቦችን እየመረጡ ለልጆቻቸው በማቅረብ ልጆች ከምንም በላይ፣ ከምንም ቀድሞ የጌታቸውን ሐቅ እንዲያውቁ ሊያግዟቸውና እራሳቸውን ከጥፋት የሚጠብቁበት እውቀት ሊያስታጥቋቸው ይገባል፡፡ ዛሬ ላይ ለተውሒድ ግንዛቤውና ፍቅሩ ያለው ትውልድ ማፍራታችን በሂደት ጠንካራ ህዝብ ለመገንባት ፅኑ መሰረት ይሆነናል፡፡
መፅሐፉ በቀጣይ እትም በተሻለ መልኩ ይወጣ ዘንድ እርምት ወይም ሀሳብ ያለው ሰው ለሚሰጠኝ ጥቆማ አስቀድሜ ከልብ አመሰግናለሁ፡፡


ሙሐመድ አሕመድ ሙነወር


ሸይኽ ሙሐመድ ኢብኑ ዐብዲል ወህሃብ አላህ ይዘንላቸውና በ 1115 ዓመተ-ሂጅራ ተወልደው በ 1206 ነው የሞቱት፡፡ ቁርኣንን ገና አስር አመት ሳይሞላቸው የሐፈዙ ሲሆን ዒልም ፍለጋ ከትውልድ ቀያቸው በመውጣት ወደ መካ፣ መዲናህ፣ አልአሕሳእ፣ በስራ፣ በግዳድ ተጉዘዋል፡፡ የተወለዱትም የሞቱትም ዑየይናህ ውስጥ ነው፣ በሳዑዲ ዐረቢያ ነጅድ ክልል፡፡ ለደዕዋ የሚያግዛቸውን እውቀት ከገበዩ በኋላ በቀጥታ ወደ ደዕዋው መስክ በመግባት ህይወታቸውን በዚሁ ላይ አሳልፈዋል፡፡ የደዕዋቸው ቀዳሚ ትኩረትም በዘመናቸው በሰፊው የተንሰራፋውን በኢስላም ስም የሚፈፀም የባእድ አምልኮ መጋፈጥ ነበር፡፡ የተውሒድ ዘመቻቸው በአላህ እገዛ ፍሬ አፍርቶ የልፋታቸውን ውጤት በአይናቸው ለማየት በቅተዋል፡፡
ሸይኹ ዐቂዳን ማስተካከል ላይ ያነጣጠሩ በርከት ያሉ ኪታቦችን ጥለው ያለፉ ሲሆን ተማሪዎቻቸውና ወራሾቻቸውም ሀላፊነታቸውን ተረክበው የድርሻቸውን ተወጥተዋል፡፡
ሸይኹ - አላህ ይዘንላቸውና - ጠላቶቻቸው እንደሚቀጥፉባቸው ከቁርኣንና ከሐዲስ ያፈነገጠ እንግዳ አስተሳሰብ አላመጡም፡፡ ለእያንዳንዱ ንግግሮቻቸው የቁርኣንና የሐዲስ ማስረጃ መጥቀሳቸውም ይህንን ሐቅ በሚገባ ያስረዳል፡፡ በየመሀሉ የቀደምት ዑለማዎችን ንግግሮች ጣል ማድረጋቸውም በቀደምቶቹ ፍኖት ላይ የሚጓዙ እንጂ አዲስ አስተሳሰብ ጠንሳሽ እንዳልሆኑ በቂ ምስክር ነው፡፡